lyrics
የልቤን ፍቃድ ጌታ ሆይ ሰጠኸኝ
የከንፈሬን ልመና አልከለከልከኝ
ሕይወትን ለመንኩህ ሕይወትህን ሰጠኸኝ
በመስቀል ላይ ሞተህ ፍቅርህን አሳየኸኝ
ጌታ ሆይ ሳበኝ ልኑር ከአንተ ጋራ
ሕይወቴ ሚያምርበት ፍሬንም የሚያፈራ
ከእቅፍ ወጪ ወዴት እሄዳለሁ
በልቤ ዙፋን ላይ አንተን አኖራለሁ
ስምን ለወንድሞች ሁልጊዜ እናገራለሁ
በጉባኤ መሀል አመሰግናለሁ
ኢየሱስ ሚለው ስም ከስሞች በላይ
የመኖሬ ምክኒያት እርሱ አይደለም ወይ
እንደ ማህተም በልቤ እንደ ማህተም በክንዴ
አኖርሀለሁ ጌታ አኖርሀለሁ ውዴ
ከፍ ካለው በላይ የምትኖር አንተ አለህና
በክብርህ ስፍራ መኖር ሕይወት ነውና
ነፍሴ ስትደክም ስትጨነቅ በሀዘን
ከቶ የለም እረፍት የለውም መጽናናት
ድምጽህን ሰማው ኑ ወደ እኔ የሚል
ያኔ ነው የተገኘው የዘለዓለም እረፍት
ከማይጠፋው ክብርህ ወርደህ የመጣኸው
በደሃ ላቤ ውስጥ ዘላለም የኖርከው
ስምህም ቅዱስ ነው ለዘለዓለም ጌታ
ምስጋና ይድረስህ ዘውትር ጥዋት ማታ
ይገባሀል ጌታ ምስጋና
ይገባሀል ጌታ አምልኮ
ይገባሀል ጌታ ውዳሴ
ደስ ብሏት ዘመረች ለአንተ ነፍሴ