เนื้อเพลง
የልቤን ፍቃድ ጌታ ሆይ ሰጠኸኝ
የከንፈሬን ልመና አልከለከልከኝ
ሕይወትን ለመንኩህ ሕይወትህን ሰጠኸኝ
በመስቀል ላይ ሞተህ ፍቅርህን አሳየኸኝ
ጌታ ሆይ ሳበኝ ልኑር ከአንተ ጋራ
ሕይወቴ ሚያምርበት ፍሬንም የሚያፈራ
ከእቅፍ ወጪ ወዴት እሄዳለሁ
በልቤ ዙፋን ላይ አንተን አኖራለሁ
ስምን ለወንድሞች ሁልጊዜ እናገራለሁ
በጉባኤ መሀል አመሰግናለሁ
ኢየሱስ ሚለው ስም ከስሞች በላይ
የመኖሬ ምክኒያት እርሱ አይደለም ወይ
እንደ ማህተም በልቤ እንደ ማህተም በክንዴ
አኖርሀለሁ ጌታ አኖርሀለሁ ውዴ
ከፍ ካለው በላይ የምትኖር አንተ አለህና
በክብርህ ስፍራ መኖር ሕይወት ነውና
ነፍሴ ስትደክም ስትጨነቅ በሀዘን
ከቶ የለም እረፍት የለውም መጽናናት
ድምጽህን ሰማው ኑ ወደ እኔ የሚል
ያኔ ነው የተገኘው የዘለዓለም እረፍት
ከማይጠፋው ክብርህ ወርደህ የመጣኸው
በደሃ ላቤ ውስጥ ዘላለም የኖርከው
ስምህም ቅዱስ ነው ለዘለዓለም ጌታ
ምስጋና ይድረስህ ዘውትር ጥዋት ማታ
ይገባሀል ጌታ ምስጋና
ይገባሀል ጌታ አምልኮ
ይገባሀል ጌታ ውዳሴ
ደስ ብሏት ዘመረች ለአንተ ነፍሴ