lyrics
ውዴ የውስጤን ማንነት አምነሽ ተቀብለሽ
በማንነቴ ውስጥ መኖሪያሽን ሰርተሽ*2
በዚህች ባልተኛ አለም አንቺን ያነገስኩሽ
ምክንያቴ እውነት ነው ከልቤ ልንገርሽ
ብኩን በበዛበት በዚህች ከንቱ አለም
ለፍቅርሽ ያበደ አንድም በቁም የለም
ሰለዚህ ልዋሽሽ ወዝሽን ላርግፈው*2
ተቀብራ የቀረች እውነት ትኖር እንደው*2
አፈር ቀልሼባት ባለጠግነትን እኔም ልታደለው
ምክንያቴ እውነት ነው*2
እውነት እልሻለው*2
የ ዘጠና ዓመት አዛውንት ድሎት ያማለለው
የወገኑን አንጡራ ሀብት ቀማኛ ሲበላው
ማነው አቤት ያለ አፍ አውጥቶ ያስጣለው
ከማባላት ውጭ ቁም ነገር የሌለው
ምክንያቴ እውነት ነው*2
እውነት እልሻለው*2
ለፍቅርሽ ያበደ አንቺን አንቺን ያለ
በአደባባይ ተሰውቶ መስዋዕትን ከፈለ
እውነት አንቺ ካለሽ ሚዛን ወዴት አለ
እውነት ተናጋሪ በሚደቆስባት
ልዩነት ሚዘራን ብኩን ተመልከቱት
ከሁለት ወንበዴዎች መሀከል እውነትን ሰቀሉት
ሐሰትን አስቀምጠው እውነትን ገደሉት
ምክንያቴ እውነት ነው*2
እውነት እልሻለው*2
ብኩን በበዛበት በዚህች ከንቱ ዓለም
ለፍቅርሽ ያበደ አንድም በቁም የለም
ብዬ የልቤን እውነታ አውጥቼ ስነግርሽ
ውሽት እንደይመስልሽ
ምክንያቴ እውነት ነው*2
እውነት እልሻለው*2
ተፃፈ በጋሻውን.ሻ