歌詞
አንድ ሰዉ ቸኩሎ ሲሄድ ወደ ፊቱ
እግሩን አደናቅፎት የመታዉ በብርቱ
የመንገድ ዳር ድንጋይ ነበር እንቅፋቱ
መቼስ
ድንጋይ አይከሰስ
ድንጋይ አይወቀስ
ህመሙን ዋጥ አድርጎ እንደምንም ታግሶ
ወደ ፊት ሄደና ካሰበበት ደርሶ
ዳግመኛ ሲመጣ ከፊቱ አብሶ
የቀደመው ድንጋይ ከመታው መልሶ
እውነት ላስተዋለ ህሊና ላለው ሰዉ
ሰዉን አንድ ድንጋይ ሁለቴ ከመታዉ
እስኪ ፍርድ ስጡ እንቅፋቱ ማነዉ
እኔ ግን ሳሰበዉ ሳስበዉ
አንዳንዴም ለድንጋይ ሰዉም እንቅፋት ነዉ