歌詞
Verse 1] (Establishing the beautiful past)እቺ ናት ኢትዮጵያ እምዬ ሀገሬ፣ታሪኳ የሚወሳ ከጥንት እስከ ዛሬ።እንግዳ ተቀባይ ሁሉን እንዳመሉ፣ማጀቷን ከፍታ ምትል ጠጡ በሉ።ያለው ተገልብጦ ከቤት ከማጀቱ፣እንግዳው እስኪጠግብ ይኖራል ከፊቱ።መች በዚህ አብቅቶ የሷ እንግዳ ክብር፣ማዕዱን አንስታ ደግሞ ውሃ ለእግር።[Verse 2] (Deepening the cultural context)ይህንን ሁሉ ታዲያ የምታደርግለት፣አይምሰላችሁ ዘመድ ስጋ የተቋጠራት።ወይም ከአካባቢው ውለታው ያለበት፣መጣሁ እንኳን ሳይል የተገኘ ድንገት።ከሷ ቤት የገባው ነው እንጂ መሽቶበት፣እቺ ናት ኢትዮጵያ... ኩራት የበዛባት።[Chorus] (The main theme, high emotional energy)እስኪ ማን ነው ሀገሬን እንዲህ የቀየራት?ሞገሷን ገፋፎ እርቃኗን ያሰቀራት?ገንቦዋን ሰባብሮ ጠላዋን ያስተዋት፣እንግዳ ነው ሲባል "ከየት መጣ" ያስባላት?እስኪ ማን ነው ሀገሬን እንዲህ የቀየራት?[Verse 3] (The painful present reality)ለጋሽ ማንነቷን ኋላ ቀር ነው ያላት፣እንጀራ በጣጥሶ ቆርጦ ያስቀረባት።ሁሉን ባንድ እንድታይ ጋርዶ የሸፈናት፣ጉያዋ ያለውን መመገብ ያቃታት።አከሌን ከእከሌ ዘርን ያስቆጠራት፣ሚገነባ መስሎ አፈራርሶ የተዋት።[Chorus] (Repeat for maximum impact)እስኪ ማን ነው ሀገሬን እንዲህ የቀየራት?ሞገሷን ገፋፎ እርቃኗን ያሰቀራት?ገንቦዋን ሰባብሮ ጠላዋን ያስተዋትእንግዳ ነው ሲባል "ከየት መጣ" ያስባላት?እስኪ ማን ነው ሀገሬን እንዲህ የቀየራት?[Bridge] (The climax, a call to the listeners)የምታውቁት ካለ ንገሩኝ እባካችሁ፣ሀገር ስትበተን ቆማችሁ ላያችሁ።ወይ እንደኔ ካለ ግራ የገባችሁ፣ያቺን ውብ ሀገሬን እንፈልግ እባካችሁ![Outro] (Softening music, fading out with hope)እኔ ግን አንድ ቀን ተስፋ አደርጋለሁ፣ያቺን ኢትዮጵያዬን ዳግም አያታለሁ።ጠላው ከነ ገንቦው፣ እንጀራው በመሶብ፣ቀርቦልኝ በላሁኝ... በፍቅር ስሰበሰብ።(Music fades out with a soft Washint/Flute solo)